በገነት አትክልት ነገር፦() ጣዕም፣ () ልማላሜ፣ () ጽጌ፣ () ሥን፣ () ፍሬ፣ () መዐዛ፣ () ቈጽል፣ ይገኛል። እንዲሁም በመዝሙረ-ዳዊት ነገር፦ () አፍቅሮ-ጸላዕት፣ () ትሕትና፣ () ሃይማኖት፣ () ተስፋ-መንግሥተ-ሰማያት፣ (፭) ተአምኖ-ኀጣውእ፣ () ስርየት፣ () ምጽዋት ይገኛል።

Friday, September 28, 2012

መዝሙር ስለ ፄዋዌ እና ሚጠት



ፄዋ ባቢሎን ይብሉከ ሶበ በጸሖሙ መከራ
በምድረ ነኪር አፅራዕነ ስባሔ እስከ ሰቀልነ እንዚራ
ወአመ ሜጥኮሙ ክርስቶስ ምስለ ዘሩባቤል መልአከ ሐራ
በክልኤ ዓመት እመንግሥተ ዳርዮስ ዳራ
ሰብሑከ በመዝሙር ዘዐሥር አውታራ

ትርጉም፦
 
የባቢሎን ምርኮኞቸ አሉኽ በደረሰባቸው ጊዜ መከራ
ምስጋናን አቋረጥን በባዕድ አገር እስከ መስቀል ደርሰን እንዚራ
በመለስካቸውም ጊዜ ክርስቶስ ካለቃ ዘሩባቤል ጋራ
በኹለተኛ ዓመት መንግሥቱ ለንጉሥ ዳርዮስ ዳራ
አመሰገኑኽ በበገና በባለዐሥር አውታራ

Saturday, September 15, 2012

ዐውደ-ፄዋዌ

በእግዚአብሔር ፈቃድ በዚህ ምክታብ የጀመርነውን ትምርት በትጋት ሊከታተሉት የሚሹ ስላገኘን፤ እንዳዲስ ልንቀጥልበት ተነሥተናል። ለዛሬ ርእሱን ስትኮረኩሙ የምታገኙትን የትሩፋንን ኹናቴ የሚያሳይ ነገር ለጥፈናል። ማብራሪያውን በፓልቶክ ጉባኤ እንሰጣለን። "የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ. የፍቅርና የሰላም ቤት" በሚባለው ክፍል። ቸር ያገናኘን።