በገነት አትክልት ነገር፦() ጣዕም፣ () ልማላሜ፣ () ጽጌ፣ () ሥን፣ () ፍሬ፣ () መዐዛ፣ () ቈጽል፣ ይገኛል። እንዲሁም በመዝሙረ-ዳዊት ነገር፦ () አፍቅሮ-ጸላዕት፣ () ትሕትና፣ () ሃይማኖት፣ () ተስፋ-መንግሥተ-ሰማያት፣ (፭) ተአምኖ-ኀጣውእ፣ () ስርየት፣ () ምጽዋት ይገኛል።

Monday, December 27, 2010

እግዚኦ ጸወነ ኮንከነ

ለዚህ ትምርት በተቃና ኹናቴ መቀጠል፤ እንዲሁም ላገራችን፣ ለወገናችን፣ ለዓለም ሕዝብ ኹሉ፣ ለግል ሕይወታችንም ጭምር፤ ከዚች ክታብ ጋራ ተያይዞ በምናገኘው መዝሙር እንጸልይ። መዝሙሩ፦ የክታቧን ርእስ ስትኮረኵሟት ይራገፍላችዃል (click on the title of this post and it will be downloaded to you)። ስንጸልይም ኑሯችንን በመዝሙሩ ከተገለጠው "ይለ-ጸሎት" ጋራ በማገናዘብ--ማለትም እኛን የመዝሙሩ፣ መዝሙሩን የእኛ ገንዘብ አድርጎ አዋሕዶ በመውሰድ--እንጸልይ። በተዋሕዶ።

ግእዝ ማንበብ የማንችል፤ ዐማርኛ መጽሐፍ ቅዱሳችንን በመጠቀም እንጸልየው። ለነገሩ፤ ግእዝ በምንማርበት ምክታብ እንደቀረቡት መልመጃዎች በምልክት የተዘጋጀ ስለኾነ፤ ደጋግመን ካጠናነው አነባበቡንም በጥቂት ጊዜ ልናውቅበት እንችላለን። የዚህን መዝሙር የምስጢር ጥልቀት ግን ትርጕሙን ስንጀምር የምናየው ይኾናል።

No comments:

Post a Comment